የመምህር ግርማ ወንድሙ መልእክት ፥ በስደት ላሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ፥ ቁጥር 31

የመንፍስ ቅዱስ የአንድነት ትውልድ።

“በይሁዳ ንጉሥ በሄሮድስ ዘመን ከአብያ ክፍል የሆነ ዘካርያስ የሚባል አንድ ካህን ነበረ፤ ሚስቱም ከአሮን ልጆች ነበረች፥ ስምዋም ኤልሳቤጥ ነበረ። ሁለቱም በጌታ ትእዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ። ኤልሳቤጥም መካን ነበረችና ልጅ አልነበራቸውም፤ ሁለቱም በዕድሜያቸው አርጅተው ነበር። እርሱም በክፍሉ ተራ በእግዚአብሔር ፊት ሲያገለግል፥ እንደ ካህናት ሥርዓት ወደ ጌታ ቤተ መቅደስ ገብቶ ለማጠን ዕጣ ደረሰበት። በዕጣንም ጊዜ ሕዝቡ ሁሉ በውጭ ቆመው ይጸልዩ ነበር። የጌታም መልአክ በዕጣኑ መሠዊያ ቀኝ ቆሞ ታየው። ዘካርያስም ባየው ጊዜ ደነገጠ፥ ፍርሃትም ወደቀበት። መልአኩም እንዲህ አለው። ዘካርያስ ሆይ፥ ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ። ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል። በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል፤ ከእስራኤልም ልጆች ብዙዎችን ወደ ጌታ ወደ አምላካቸው ይመልሳል።” የሉቃስ ወንጌል ፤ ምዕራፍ 1 ቁር 5 : 16

የመምህር ግርማ ወንድሙ መልእክት ፥ በስደት ላሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ፥ ቁጥር 30

ከቤተልሔም የወጣ ትውልድ እና፤ ከቅዱስ ቁርባን የራቀ ትውልድ ውጤቱ።

“እንዲህም ሆነ፤ መሳፍንት ይፈርዱ በነበረ ጊዜ በአገሩ ላይ ራብ ሆነ። አንድ ሰውም ከሚስቱና ከሁለቱ ልጆቹ ጋር በሞዓብ ምድር ሊቀመጥ ከቤተ ልሔም ይሁዳ ተነሥቶ ሄደ። የሰውዮውም ስም አቤሜሌክ፥ የሚስቱም ስም ኑኃሚን፥ የሁለቱም ልጆች ስም መሐሎንና ኬሌዎን ነበረ፤ የቤተ ልሔም ይሁዳም የኤፍራታ ሰዎች ነበሩ። ወደ ሞዓብም ምድር መጡ በዚያም ተቀመጡ። የኑኃሚንም ባል አቤሜሌክ ሞተ፤ እርስዋና ሁለቱ ልጆችዋ ቀሩ። እነርሱም ከሞዓባውያን ሴቶች ሚስት አገቡ፤ የአንዲቱ ስም ዖርፋ የሁለተኛይቱም ስም ሩት ነበረ። በዚያም አሥር ዓመት ያህል ተቀመጡ። መሐሎንና ኬሌዎንም ሁለቱ ሞቱ፤ ሴቲቱም ከሁለቱ ልጆችዋና ከባልዋ ተለይታ ቀረች። እርስዋም በሞዓብ ምድር ሳለች እግዚአብሔር ሕዝቡን እንደ ጐበኘ እንጀራም እንደ ሰጣቸው ስለ ሰማች፥ ከሞዓብ ምድር ልትመለስ ከሁለቱ ምራቶችዋ ጋር ተነሣች። እርስዋም ከሁለቱ ምራቶችዋ ጋር ከተቀመጠችበት ስፍራ ወጣች፤ ወደ ይሁዳም ምድር ሊመለሱ በመንገድ ሄዱ። ኑኃሚንም ምራቶችዋን። ሂዱ፥ ወደ እናቶቻችሁም ቤት ተመለሱ፤ በእኔና በሞቱት እንዳደረጋችሁ፥ እግዚአብሔር ቸርነት ያድርግላችሁ። እግዚአብሔር በየባላችሁ ቤት ዕረፍት ይስጣችሁ አለቻቸው። ሳመቻቸውም፤ ድምፃቸውንም ከፍ አድርገው አለቀሱ። እነርሱም። ከአንቺ ጋር ወደ ሕዝብሽ እንመለሳለን አሉአት።” መጽሐፈ ሩት ፤ ምዕራፍ 1 ቁር 1 : 10

የመምህር ግርማ ወንድሙ መልእክት ፥ በስደት ላሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ፥ ቁጥር 29

ቅዱስ ቁርባን፥ ለምን እና በምን ግዜ ይወስዳል።

“ኢየሱስም እንዲህ አላቸው። የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም በእኔ የሚያምንም ሁልጊዜ ከቶ አይጠማም። ነገር ግን አይታችሁኝ እንዳላመናችሁ አልኋችሁ። አብ የሚሰጠኝ ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል፥ ወደ እኔም የሚመጣውን ከቶ ወደ ውጭ አላወጣውም፤ ፈቃዴን ለማድረግ አይደለም እንጂ የላከኝን ፈቃድ ለማድረግ ከሰማይ ወርጃለሁና። ከሰጠኝም ሁሉ አንድን ስንኳ እንዳላጠፋ በመጨረሻው ቀን እንዳስነሣው እንጂ የላከኝ የአብ ፈቃድ ይህ ነው። ልጅንም አይቶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወትን እንዲያገኝ የአባቴ ፈቃድ ይህ ነው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።” ” የዮሐንስ ወንጌል ፤ ምዕራፍ 6 ቁር 35 : 40

መምህር ግርማ ወንድሙ • ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ • ቁጥር 20

“ከባላጋራዬ ፍረድልኝ…”

የሉቃስ ወንጌል፥ምዕራፍ 18 ቁር 3

“እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልወደዱት መጠን እግዚአብሔር የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው፤ ዓመፃ ሁሉ፥ ግፍ፥ መመኘት፥ ክፋት ሞላባቸው፤ ቅናትን፥ ነፍስ መግደልን፥ ክርክርን፥ ተንኰልን፥ ክፉ ጠባይን ተሞሉ፤ የሚያሾከሹኩ፥ ሐሜተኞች፥ አምላክን የሚጠሉ፥ የሚያንገላቱ፥ ትዕቢተኞች፥ ትምክህተኞች፥ ክፋትን የሚፈላለጉ፥ ለወላጆቻቸው የማይታዘዙ፥የማያስተውሉ፥ ውል የሚያፈርሱ፥ ፍቅር የሌላቸው፥ ምሕረት ያጡ ናቸው፤ እንደነዚህ ለሚያደርጉት ሞት ይገባቸዋል የሚለውን የእግዚአብሔርን ሕግ እያወቁ እነዚህን ከሚያደርጉ ጋር ይስማማሉ እንጂ አድራጊዎች ብቻ አይደሉም።”

ወደ ሮሜ ሰዎች ፥ምዕራፍ 1 ቁር 28 – 32

“ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ።”

1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕራፍ 16 ቁር 13

የመምህር ግርማ ወንድሙ መጽሐፍ “በማለዳ መያ`ዝ” የምረቃ ሥነ ሥርዓት።

“በማለዳ መያ`ዝ” የሚለው አዲሱ የመምህር ግርማ ወንድሙ መጽሐፍ በገበያ ላይ ወጥቶአል፥፥

The new spiritual book from Memehir Girma Wondimu is now published. If you live the in Washington DC area, you can buy the book from Habesha Market and Restaurant, 1919 9th Street NW, Washington DC.Phone (202) 232-1919.

If you live in the Denver, Colorado or Minnesota area, you can get the book from Mr. Bereket Phone no: (617) 309-7840.

መምህር ግርማ ወንድሙ • ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ • ቁጥር 19

“ብዙዎች ለክርስቶስ መስቀል ጠላቶቹ ሆነው ይመላለሳሉና፤ ብዙ ጊዜ ስለ እነርሱ አልኋችሁ፥ አሁንም እንኳ እያለቀስሁ እላለሁ። መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው።”

ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች ፥ምዕራፍ 3 ቁር 18 – 19

“የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና።”

1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ፥ምዕራፍ 1 ቁር 18

“ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ።”

1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕራፍ 16 ቁር 13

መምህር ግርማ ወንድሙ • ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ • ቁጥር 18

“ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን ዓለምም በሞላው በክፉው እንደ ተያዘ እናውቃለን።”

የዮሐንስ መልእክት፤ ምዕራፍ 5 ቁር 19

“ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ።” — 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕራፍ 16 ቁር 13

መምህር ግርማ ወንድሙ • ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ • ቁጥር 17

ትንሹ ልጅ እና የዘመኑ መንፈስ

“እንዲህም አለ። አንድ ሰው ሁለት ልጆች ነበሩት። ከእነርሱም ታናሹ አባቱን። አባቴ ሆይ፥ ከገንዘብህ የሚደርሰኝን ክፍል ስጠኝ አለው። ገንዘቡንም አካፈላቸው። ከጥቂት ቀንም በኋላ ታናሹ ልጅ ገንዘቡን ሁሉ ሰብስቦ ወደ ሩቅ አገር ሄደ፥ ከዚያም እያባከነ ገዘቡን በተነ። ሁሉንም ከከሰረ በኋላ በዚያች አገር ጽኑ ራብ ሆነ፥ እርሱም ይጨነቅ ጀመር። ሄዶም ከዚያች አገር ሰዎች ከአንዱ ጋር ተዳበለ፥ እርሱም እሪያ ሊያሰማራ ወደ ሜዳ ሰደደው።”

የሉቃስ ወንጌል ፥ ምዕራፍ 15 ቁር 11 እስከ 15

አባታችሁ ማነው? አባታችሁ እግዛብሄርን አትርሱ፡፡

“እንወቅ፤ እናውቀውም ዘንድ እግዚአብሔርን እንከተል፤ እንደ ወገግታም ተዘጋጅቶ እናገኘዋለን፤ እንደ ዝናብም ምድርንም እንደሚያጠጣ እንደ መጨረሻ ዝናብ ይመጣል።”

ትንቢተ ሆሴዕ ፥ ምዕራፍ 6 ቁር 3

Video

መምህር ግርማ ወንድሙ • ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ • ቁጥር 16

እንግዲህ እናንተ የዘሪውን ምሳሌ ስሙ። የመንግሥትን ቃል ሰምቶ በማያስተውል ሁሉ፥ ክፉው ይመጣል፥ በልቡ የተዘራውንም ይነጥቃል፤ በመንገድ ዳር የተዘራው ይህ ነው።

የማቴዎስ ወንጌል ፥ ምዕራፍ ፲፫ ቁር ፲፰

Video

መምህር ግርማ ወንድሙ • ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ • ቁጥር 15

እናንተ የአባታችሁን ሥራ ታደርጋላችሁ አላቸው። እኛስ ከዝሙት አልተወለድንም አንድ አባት አለን እርሱም እግዚአብሔር ነው አሉት።

የዮሐንስ ወንጌል ፥ ምዕራፍ ፰ ቁር ፵፩

Video

መምህር ግርማ ወንድሙ • ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ • ቁጥር 13

ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው፥ ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፤ ወደ ምድር ተጣለ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ። ታላቅም ድምፅ በሰማይ ሰማሁ እንዲህ ሲል። አሁን የአምላካችን ማዳንና ኃይል መንግሥትም የክርስቶስም ሥልጣን ሆነ፥ ቀንና ሌሊትም በአምላካችን ፊት የሚከሳቸው የወንድሞቻችን ከሳሽ ተጥሎአልና። እነርሱም ከበጉ ደም የተነሣ ከምስክራቸውም ቃል የተነሣ ድል ነሡት፥ ነፍሳቸውንም እስከ ሞት ድረስ አልወደዱም።

የዮሐንስ ራእይ ፤ ምዕራፍ ፲፪ ቁር ፱ እስከ ፲፩

Video

መምህር ግርማ ወንድሙ • ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ • ቁጥር 12

እግዚአብሔርም በጳውሎስ እጅ የሚያስገርም ተአምራት ያደርግ ነበር፤ ስለዚህም ከአካሉ ጨርቅ ወይም ልብስ ወደ ድውዮች ይወስዱ ነበር፥ ደዌያቸውም ይለቃቸው ነበር ክፉዎች መናፍስትም ይወጡ ነበር።

የሐዋርያት ሥራ ፤ ምዕራፍ ፲፱ ቁር ፲፩ እስከ ፲፪

Video

መምህር ግርማ ወንድሙ • ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ • ቁጥር 11

በነቢዩ በኢሳይያስ ቃል መጽሐፍ። የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ፤ ዐዘቅቱ ሁሉ ይሙላ ተራራውና ኮረብታውም ሁሉ ዝቅ ይበል፥ ጠማማውም የቀና መንገድ ይሁን፥ ሸካራውም መንገድ ትክክል ይሁን፤ ሥጋም የለበሰ ሁሉ የእግዚአብሔርን ማዳን ይይ ተብሎ እንደ ተጻፈ ለኃጢአት ስርየት የንስሐን ጥምቀት እየሰበከ በዮርዳኖስ ዙሪያ ወዳለችው አገር ሁሉ መጣ።

የሉቃስ ወንጌል ፥ ምዕራፍ ፫ ቁር ፫ እስከ ፮

የመምህር ግርማ ወንድሙ መልእክት ፥ በስደት ላሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ፥ ቁጥር 27

በክርስቶስ ስጋና ደም በኩል፥ እግዚአብሔር ቃልህን ያከብራል።

“እግዚአብሔርም አብራምን አለው። ከአገርህ ከዘመዶችህም ከአባትህም ቤት ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ። ታላቅ ሕዝብም አደርግሃለሁ፥ እባርክሃለሁ፥ ስምህንም አከብረዋለሁ፤ ለበረከትም ሁን፤ የሚባርኩህንም እባርካለሁ፥ የሚረግሙህንም እረግማለሁ፤ የምድር ነገዶችም ሁሉ በአንተ ይባረካሉ።” ኦሪት ዘፍጥረት ፤ ምዕራፍ 12 ቁር 1 : 3

የመምህር ግርማ ወንድሙ መልእክት ፥ በስደት ላሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ፥ ቁጥር 26

ከጠላት በቅዱስ ቁርባን እንዴት እንደምንድን፡፡

“በልዑል መጠጊያ የሚኖር ሁሉን በሚችል አምላክ ጥላ ውስጥ ያድራል። እግዚአብሔርን። አንተ መታመኛዬ ነህ እለዋለሁ፤ አምላኬና መሸሸጊያዬ ነው፥ በእርሱም እታመናለሁ። እርሱ ከአዳኝ ወጥመድ ከሚያስደነግጥም ነገር ያድንሃልና። በላባዎቹ ይጋርድሃል፥ በክንፎቹም በታች ትተማመናለህ፤ እውነት እንደ ጋሻ ይከብብሃል። ከሌሊት ግርማ፥ በቀን ከሚበርር ፍላጻ፥ በጨለማ ከሚሄድ ክፉ ነገር፥ ከአደጋና ከቀትር ጋኔን አትፈራም። በአጠገብህ ሺህ በቀኝህም አሥር ሺህ ይወድቃሉ፤ ወደ አንተ ግን አይቀርብም። በዓይኖችህ ብቻ ትመለከታለህ፥ የኃጥኣንንም ብድራት ታያለህ። አቤቱ፥ አንተ ተስፋዬ ነህና፤ ልዑልን መጠጊያህ አደረግህ። ክፉ ነገር ወደ አንተ አይቀርብም፥ መቅሠፍትም ወደ ቤትህ አይገባም። በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል። በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ። በእኔ ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ።vይጠራኛል እመልስለትማለሁ፥ በመከራውም ጊዜ ከእርሱ ጋራ እሆናለሁ፤ አድነዋለሁ አከብረውማለሁ። vረጅምን ዕድሜ አጠግበዋለሁ፥ ማዳኔንም አሳየዋለሁ። መዝሙረ ዳዊት ፤ ምዕራፍ 91 ቁር 1 : 16

የመምህር ግርማ ወንድሙ መልእክት ፥ በስደት ላሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ፥ ቁጥር 24

በመለኮታዊ ሚስጢሩ እደጉ።

“የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ። ስለ ክፉ ምኞት በዓለም ካለው ጥፋት አምልጣችሁ ከመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንድትሆኑ፥ በእነዚያ ክብርና በጎነት የተከበረና እጅግ ታላቅ የሆነ ተስፋን ሰጠን። ስለዚህም ምክንያት ትጋትን ሁሉ እያሳያችሁ በእምነታችሁ በጎነትን ጨምሩ፥ በበጎነትም እውቀትን፥ በእውቀትም ራስን መግዛት፥ ራስንም በመግዛት መጽናትን፥ በመጽናትም እግዚአብሔርን መምሰል፥ እግዚአብሔርንም በመምሰል የወንድማማችን መዋደድ፥ በወንድማማችም መዋደድ ፍቅርን ጨምሩ። እነዚህ ነገሮች ለእናንተ ሆነው ቢበዙ፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ሥራ ፈቶችና ፍሬ ቢሶች እንዳትሆኑ ያደርጉአችኋልና፤ እነዚህ ነገሮች የሌሉት ዕውር ነውና፥ በቅርብም ያለውን ብቻ ያያል፥ የቀደመውንም ኃጢአቱን መንጻት ረስቶአል። 2ኛ የጴጥሮስ መልእክት ምዕራፍ ፥ ምዕራፍ 1 ቁር 2 : 9

“በማለዳ መያ`ዝ” አዲሱ የመምህር ግርማ ወንድሙ መጽሐፍ በገበያ ላይ ወጥቶአል፥፥

ውንድሞችና እህቶች ፥”በማለዳ መያ`ዝ” የሚለው አዲሱ የመምህር ግርማ ወንድሙ መጽሐፍ በገበያ ላይ ወጥቶአል፥፥

The new spiritual book from Memehir Girma Wondimu is now published.

If you live the in Washington DC area, you can get the book from Habesha Market and Restaurant, 1919 9th Street NW, Washington DC.Phone (202) 232-1919.

If you live the Minnesota area, you can get the book from Mr. Bereket Phone (617) 309-7840.